tg-me.com/fiqshafiyamh/1372
Last Update:
የሙሐባ ነገር የምርጫ አይደለም። እናት በሥጋ የራቃት ልጇን የሚያስታውሳትን ነገር መዘከሯ አማራጭ የሌለው ግዳጅ ከሆነ…
ልብሱን ስታይ፣ ፎቶውን ስትመለከት፣ ፍራሹን ስትዳስስ፣ የተወለደበትን ቀን ስታስብ፣ የሞተበት ቀን ሲመጣ፣ ጓደኞቹን ስታገኝ ወ. ዘ. ተ. ልጇን ማስታወሷ፣ ስለርሱ ማውራቷ፣ ደስታውን አውጠንጥና መደሰቷ፣ ሀዘኑን አስባ ማልቀሷ የማይቀር ከሆነ. የኛውም ጉዳይ አማራጭ ያለው አይደለም ማለት ነው!
ሰው የሚወደውን አካል የሚያስታውሱ ሁኔታዎቹን ማሰቡ ቅሮት ከሌለው የሰዪዲን [ሰለላሁዐለይሂ ወሰለም] ልደት ማሰብ አማራጭ የሌለው በፍቅር ህግ የወጀበ ግዴታ ነው። ጉዳዩ ከተክሊፍ ውጪ የሆነ አስገዳጅ ነገር ነው። ሰው እንዴት የግል ህይወቱን ወሳኝ ክስተቶች ወይም የሚወዳቸውን የህይወት አጋጣሚዎች ሊረሳ ይችላል?!
እንዴታ! መወለዳቸው ያመጣልንን በረከትና ፀጋ መርሳት አንችልማ! አመስግነን የማንጨርሰው ታላቅ ስጦታ ናቸዋ! ረስተናቸው ሳይሆን የምናወሳቸው የቀልባችን ነጋሲ፣ የጌታችን ፀጋ ናቸዋ!
የምወዳችሁ ሁሉ ለተፈቃሪያችን የመውሊድ ዝክር እንኳን አደረሳችሁ!
BY Tofik Bahiru
![](https://photo.tg-me.com/u/cdn4.cdn-telegram.org/file/OGHyNjOcv8pIi2lRjXV31MbWtmn6wA02zIP88-fQkZZYI9Xk00XH4V9mX_6nUAntJUmpRe5n118A4kLGCDQBeGjYWki2nbd0i_MgY3V2GO4g14pXKVES57a4x9V2ZbivHYB3N4Jzn6IYLbezOoLw6fRzHROTyShtJSZGWf5I4kO9cNs-ZLFQf2kblNf0SRRe0TT8dwcY3cOSgFWsj0mEd_G8XUHqSEdZVZsEEkAucnOItTOKm-Vh9jGhEV1g4WdwArON_rQNAlb1iguoqF0eXTuSvbvrKuFSHo84762RERccR0ZBOqvn1NwoF8uIaOAAmYr6bqoVG6aHC1nvRsHPDg.jpg)
Share with your friend now:
tg-me.com/fiqshafiyamh/1372